ቤት ፈረሳ በኢትዮጵያ
የሸገር ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣናት "ሕገ ወጥ" ያሏቸውን መኖሪያ ቤቶች ሲያፈርሱ "ማኅበራዊ ቀውስ" መፈጠሩን ባያምኑም ዜጎች ብርቱ ችግር ገጥሟቸዋል። ቤታቸው የፈረሰባቸው ዜጎች አቤቱታ የቀረበላቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኃላፊዎች የተሳተፉበት ውይይት የእርምጃውን አመክንዮ እና ዳፋ ይፈትሻል
በአዲስ አበባ ዙሪያ የነበሩ ከተሞችን አንድ ላይ በማዋቀር እንደ አዲስ የተቋቋመው የሸገር ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣናት "ሕገ ወጥ" ያሏቸውን የመኖሪያ ቤቶች እያፈረሱ ነው። የሚፈርሱት “ሕጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ የሌላቸው” የተባሉ ግንባታዎች ሲሆኑ አብዛኞቹ የመኖሪያ ቤቶች ናቸው። "በተለይም ከ2005 ዓ.ም. በኋላ የተገነቡ ቤቶች እንዲፈርሱ በተወሰነው መሠረት" እርምጃው እየተወሰደ እንደሚገኝ የሸገር ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣናት ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ መሠረት "ከቤቶቹ ባለቤቶች ጋር በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ ውይይት ተደርጎ በቂ ግንዛቤ" እንዲፈጠር መደረጉን ባለሥልጣናቱ ተናግረዋል።
ምንጭ Dw
Comments
Post a Comment